“ፕሮቴስታንቱን ምን ነካው?”

ከጥቂት ወራት በፊት በኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ህብረትና በመሰረት ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሐሰተኛና አስጸያፊ ተብለው መግለጫ የተሰጠባቸው አዳዲስ አገልጋዮችና አገልግሎቶች እስካሁን ድረስ በስፋት እያነጋገሩ ይገኛሉ። ዶ/ር ወዳጄነህ ሰሞኑን በኤክሶደስ ሾው ላይ በሰጡት ቃለ ምልልስ ምክንያት ይኸው የ“ሐሰተኛ ነብያት” ጉዳይ ትኩስ ትኩረት አግኝቷል። በዚህ ጽሁፍ “ሰው የሚዘራውን ያንኑ ደግሞ ያጭዳል” የሚለውን መጽሃፍ ቅዱሳዊ ህግ መሰረት አድርጌ የዚህን እያነጋገረ ያለ ችግር መንስኤና መፍትሔ ለመመርመር እሞክራለሁ። ዶ/ር ወዳጄነህ ላነሱት “ፕሮቴስታንቱን ምን ነካው?” ላሉት ጥያቄም መልስ አፈላልጋለሁ።